ትኩስ ዜና
ኢህአዴግ
ኢህአዴግ አገር የመምራት ሃላፊነትን ከተረከበ ጊዜ ጀምሮ ከውስጥም ከውጭም የሚነሱ በርካታ ውጣ ውረዶችን ያስተናገደ ድርጅት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከአገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር የሚጣጣምና የህዝባችንን ሁለንተናዊ መለወጥ ታሳቢ ያደረገ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ስርዓት በማራመድ በውጭ ሃይል ተፅእኖ የሚጠመዘዝ ድርጅት አለመሆኑን ገና በጠዋቱ በተግባር ያሳየ ድርጅት ነው፡፡
ከደርግ ውድቀት ማግስት አገራችን የመበታተን ስጋት ውስጥ የነበረችበት ሁኔታ ቢኖርም መላ የሃገሪቱን ህዝቦች በማስተባበርና በብስለት በመምራት ዴሞክራሲያዊ አንድነቷ በፅኑ መሰረት ላይ እየተገነባ እንዲዘልቅ አስችሏል። ህገ መንግስታችን የአንድነታችንና የመከባበራችን ማሰሪያ ውል እንዲሆን በሚያስችል መልኩ በህዝብ ሙሉ ተሳትፎ ተቀርፆ በመፅደቁ ያንን የመበታተን ስጋት ተሻግረን በጋራ ለዘላቂ ለውጥ መረባረብ ጀምረናል።
ዜና
የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሞችን በጥልቀት በመገምገም ቀጣይ የኢኮኖሚ አቅጣጫዎችን አስቀመጠ።
የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሚያዚያ 28/2011 ዓም ባካሄደው ስብሰባ ያለፉት ዓመታትን የኢኮኖሚ ዘርፍ አፈፃፀም በዝርዝር ከገመገመ በኋላ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሞችን በማስቀመጥ ስብሰባውን አጠናቋል። ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው ከ2003 እስከ 2010 ዓም በአገሪቱ የተመዘገበውን የኢኮኖሚ አፈፃፀም የገመገመ ሲሆን በእነዚህ ዓመታት ውስጥ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት በአማካይ የ9.6 እድገት ማሳየቱን በዚህም የግብርና ዘርፍ የ5.7 በመቶ፣ የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደግሞ የ19.1 በመቶ እንዲሁም የአገልግሎት ዘርፍ 10.3 በመቶ እድገት ማስመዝገቡን ተመልክቷል።
ተጨማሪ ያንብቡ…
የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ
የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር(ኢህአዴግ) ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ከዛሬ ሚያዝያ 28ቀን 2011 ዓም ጀምሮ ስብሰባውን ማካሄድ ጀምሯል፡፡ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴው በድርጅታዊና ወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት በማካሄድ ውሳኔዎችንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ…
“በኢሕአዴግ ምክር ቤት ስብሰባዎች የመሳተፍ ዕድላችን መስፋት በክልላዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጥልቀት እንድንወያይ አስችሎናል ” አጋር ፓርቲዎች
የድርጅቶቹ አመራሮች ላለፉት ሁለት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባን አስመልክቶ ለሚዲያዎች መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የሶማሌ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን ወክለው መግለጫውን የሰጡት ምክትል ርዕሰ መስተዳደሩ አቶ አደም ፋራህ፣ የአፋር ዴሞክራሲያዊ ፓርቲን ወክለው በመወከል ደግሞ የድርጅቱ ምክትል ሊቀ መንበርና የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ አወል አርባ፣ አቶ አሻድሊ ሃሰን የቤንሻንጉል ክልል ፕሬዝዳንትና የቤንሻንጉል ጉምዝ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሊቀ መንበር፣ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን ወክለው የፓርቲው ሊቀ መንበርና የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ኡመድ ኡጁሉና የሀረሪ ብሄራዊ ሊግን በመወከል ደግሞ የሊጉ ሊቀ መንበርና የሀረሪ ክልል ፕሬዝዳነት አቶ ኦርዲን በድሪ ናቸው፡
ተጨማሪ ያንብቡ…
የኢሕአዴግ ምክር ቤት ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎችን እና ያለፉትን ወራት የእቅድ አፈፃፀም በጥልቀት ገምግሞ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መደበኛ ስብሰባውን አጠናቀቀ።
የኢሕአዴግ ምክር ቤት ከሚያዚያ 7 - 8 /2011 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ሀገራዊ የለውጥ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና የተከናወኑ የፖለቲካና የድርጅት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግሟል። ባለፈው አንድ አመት በተለይም 11ኛው የኢሕአዴግ ጉባኤ ከተካሄደበት መስከረም ወር ጀምሮ የጉባዔውን ዋናዋና ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች መሰረት በማድረግ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት ያስቻሉ ተጨባጭ እርምጃዎች ሲወሰዱ መቆየታቸውን ምክር ቤቱ በዝርዝር ተመልክቷል። የፖለቲካ ምህዳሩን ከማስፋት አኳያ የተሰሩ ዘርፈ ብዙ ስራዎች መኖራቸውን፤ እህት እና አጋር ፓርቲዎች እያደረጓቸው ያሉ እንቅስቃሴዎች በመልካም ጅምርነት የገመገመው ምክር ቤቱ በቅርቡ ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የተፈረመው የቃል ኪዳን ሰነድ በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ቦታ ያለው እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ ኢህአዴግ የቃል ኪዳን ሰነዱን አክብሮ በመንቀሳቀስ ሃላፊነቱን በተሟላ መልኩ እንዲወጣ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ህገ መንግስቱን፤ የሀገሪቱን ህጎች አክብረው በሰላማዊ የሀሳብ ትግል ብቻ በመድብለ ፓርቲ ስርዓቱ ውስጥ ያለባቸውን ሃላፊነት ተረድተው እንዲንቀሳቀሱ ጥሪውን አስተላልፏል።
ተጨማሪ ያንብቡ…
መጣጥፎች
እንደገና ወደ ኋላ ለማን በጀ?
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች ላይ የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት የክልሉን ልማት ወደ ኋላ ለመመለስ ብቻ ሳይሆን ለዘመናት በመተሳሰብና በመቻቻል አብሮ ከኖረው ከወንድሙ የኦሮሞ ህዝብ ጋር ያለውን ግንኙነት ለማሻከርና እርስ በእርስ የጥርጣሬ መንፈስ እንዲፈጠር በማድረግ የመተባበርና የመደጋገፍ አቅሙን ለማዳከም ታልሞ የተሰራ ሴራ ነው፡፡ በአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘናት የተጀማመሩና የኢኮኖሚ ምህዋሩን አንድ ደረጃ ማሳደግ የሚያስችሉ ልማቶችን ከመደገፍና ደጀን ከመሆን ይልቅ ኢ-ምክንያታዊ በሆኑ ነገሮች ሰበቦችን በመፍጠር ብሔርን መሰረት አድርገው ሁከትና አለመረጋጋት እንዲፈጠር በማድረግ አንዳንድ አፍራሽ ኃይሎች መንግስትን የማዳከም ስራ ላይ ተጠመደዋል፡፡ የሰው ህይወት እንዲጠፋ፣ የህዝብና መንግስት ንብረቶችን ማውደም፣ እንዲሁም ይህንኑ ግርግር መነሻ በማድረግ በዝርፊያና ስርቆት ወንጀሎች ላይ በመሰማራት በህገ ወጥ መንገድ የግል ሀብታቸውን ለማፍራት የሚኳትኑ ጥቂት እፉኝቶች የሌት ተቀን ስራቸው አድርገውታል፡፡
ለሚወረወርልን እሳት ጭድ እየመገብነው ነው ወይስ ውሃ እየቸለስንበት?
በዚህ ይህ የኔ አካባቢ ነው፣ አንተ መጤ ነህ፣ ውጣልኝ/ውጭልኝ እስከ መባባል ተደርሶ፤ የሰው ህይወት እየጠፋና በርካቶች ለዘመናት ከኖሩበት የትውልድ ቀዬአቸው እየተፈናቀሉ ነው፡፡ ይህ ግጭት እውነትም በህዝቦች መካከል እየተፈጠረ ያለ ግጭት ነው ወይ? ሲባል ሁሉም አፉን ሞልቶ በጭራሽ፤ እንዴት ተደርጎ፤ በተድላ ጊዜ በደቦ አመርተን ለአገር የምንተርፍ፣ በችግራችን ጊዜ ደግሞ አንድ ቂጣ ተካፍለን በልተን አድረን ክፉ ደጉን አብረን ያሳለፍን፤ አንድ እናት ገቢያ ስትሄድ የአንዷን እናት ጡት ለሁለት ጠብተን ያደግን ሰዎች ምን ቆርጦን ጦር እንማዘዛለን? እንላለን፡፡ ከግጭት መልስ በየአካባቢው የሚደረዱ ህዝባዊ ውይይቶች ላይም አዘውትረን የምንሰማው ይህንኑ ነው፡፡ ደግሞም ሀቅ ነው፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚያጋጨን? ሲባል መልሱ ግልጽ ነው፡፡ ያንን አብሮነታችንን አፍርሶ እርስ በእርስ አባልቶ ሊያጣፋን የሚሻ የጋራ ጠላታችን ወይም በግጭት ውስጥ ጥቅም የሚፈልግ ቁንጽል ፖለቲከኛ ወይም ብሄሩን መደበቂያ አድርጎ ከተጠያቂነት ለመሸሽ ላይ ታች የሚል ሌባ/ሙሰኛ ነው፡፡ ሲጠቃለል ግን የኛም ሆነ ከውጭ የመጣ ወገንን ደም በማቃባት ትርፍ የሚፈለግ ወይም የሚደሰት ያው ጠላታችን ነው፡፡
አብሮነታችንን ማን አየብን?
ኢትዮጵያ ሰላም ያለባት ሀገር እየመሰለች፤ ነገር ግን በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ቁጥር በዓለም አቀፍ ደረጃ የመጀመሪያውን ቁጥር ከመያዝ ባሻገር በዚህ በኩል በእርስ በእርስ ጦርነት እየታመሱ ካሉት ሶርያ፣ ሶማሊያ፣ የመንና ደቡብ ሱዳን ጋር አብሮ ስሟ መጠራቱ ለኢትዮጵያዊ ማንነት የማይመጥን የአብሮነትየመደጋገፍ ባህላችንን የሚያጠለሽና በሁላችንም ዘንድ በእጅጉ ሀዘኔታን የሚፈጥር ነው፡፡
ከ‹‹እኔ ብቻ›› ስሜት መሻገር ይገባል!!
በመደመር እሳቤ የጀመርነው ሁሉን አቀፍ አገራዊ ለውጥ እንደ ንብ ታታሪ ሆኖ በመስራት ለውጡን ዳር ማድረስ ከሁሉም ዜጋ የሚጠበቅ ሀላፊነት ነው፡፡ በእኛነት ስሜት በመደራጀት በአገራችን ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በጋራ በመታገል ዛሬ የደረስንበት ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ ተችሏል፡፡ በተባበረ አንድነታችን ያቀነቀንለት የለውጥ ዝማሬ አልፎ አልፎ አንዳንድ መሰናክሎች እያስተናገደ ይገኛል፡፡ በቁልቁለት መንገድ ለማስገባት ከኋላ የሚገፉ ከፊት የሚስቡ የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚሯራጡ ሃይሎች እዚም እዚያም ይስተዋላሉ፡፡ የተጀመረውን የለውጥ ጉዞ ወደ ኋላ ለመመለስ በርካታ ወጥመዶች እየዘረጉ ይገኛሉ፡፡ በብሄሮች መካከል ያለውን ልዩነት በማጉላት በሕዝቦች መካከል ጭቅጭቅና ንትርክ ለመፍጠር የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ ይስተዋላሉ፡፡ በበርካታ ውጣውረድ ታልፎ የተገኘውን የለውጥ ጉዞ ለማስቀጠል አልፎ አልፎ የሚፈጠሩ ችግሮችን በሠለጠነ እና በሰከነ መንገድ በመፍታት የዴሞክራሲ ባህላችንንም ማሳደግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡
የፌዴራል ስርዓቱ ሁሉንም ፍላጎቶች ማስተናገድ የሚችል ነው!
እነአሜሪካና ስዊዘርላንድ ፌዴራላዊ ስርዓትን ተቀብለው መተግበር ከጀመሩ ምዕተ አመት አስቆጥረዋል። እንደተባለው ስርዓቱ ሀገርን አደጋ ውስጥ የሚጥልና አንድነትን የሚያጠፋ ቢሆን ኖሮ ዛሬ አሜሪካም ሆነ ስዊዘርላንድ የሚባሉ አገራትን ላናይ እንችል ነበር። አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ1789 በህገመንግስት የተረጋገጠ ፌደራላዊ ስርዓትን በሀገሯ ላይ እውን አድርጋለች። ስዊዘርላንድ ደግሞ እ.ኤ.አ በ1848 ስርዓቱን በህገመንግስቷ እውቅና ሰጥታ ዘርግታለች። ጀርመንም እ.ኤ.አ.በ1871 ፌዴራላዊ መንግስትን ይፋ አድርጋለች። በመቀጠልም ካናዳ፣ ቤልጂየም፣ ህንድ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ናይጄሪያ፣ ሱዳን፣ አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ ሜክሲኮ፣ የቀድሞዋ ዩጎዝላቪያ የተለያዩ ግዛቶች፣ ቼኮስሎቫኪያ፣ ከኮሚኒዝም መፈራረስ በኋላ የቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት ወደ ፌዴራል ስርዓት በሂደት እንደተቀላቀሉ የዘርፉ ምሁራን ከጻፏቸው ሰነዶች መረዳት ይቻላል።
